African Storybook
Menu
አባቱን የታደገው ጥላሁን
ከድር ኢብራሂም
Benjamin Mitchley
Amharic
በዱሮ ዘመን ከአባቱ ጋር የሚኖር ጥላሁን የተባለ ልጅ ነበር። የጥላሁን አባት አቶ አበበ ይባላሉ፡፡
እናም አቶ አበበ ሁሌ ወደ ቤታቸው የሚመጡት ሲጠጡ ያመሹና ነበር።
ሁሌ ሰክረው በመጡ ቁጥር መንደሩን በጩኸት ያናውጡት ነበር፡፡ ''ሰፈር፥ሰፈር! ኡ ኡ ኡ! እርዱኝ! ጅብ ሊበላኝ ነው!'' እያሉ ይጮሀሉ፡
የአቶ አበበን ጩኸት የሰሙ የሰፈሩ ሰዎች አቶ አበበን ለመርዳት ጦርና ገጀራ ይዘው ይወጣሉ። ነገር ግን ወጥተው ሲያዩት ምንም ጅብ የሚባል ነገር የለም። ከዚያም ሰፈርተኛው ሁሉ ''ምን አደረግነው ይህ ሰው? እንቅልፍ አሳጣን እኮ'' እያሉ ወደየቤቶቻቸው ይመለሳሉ፡፡
የጥላሁን አባት መስከራቸውንና ለእርዳታ መጮሃቸውን ቀጠሉ። ሰፈርተኛውም አቶ አበበን ለመርዳት ጦርና ገጀራ ይዞ ይወጣል፡፡  ነገር ግን ሁልጊዜም ተመሳሳይ ታሪክ ነው፤ እያሾፉባቸው ነበር።
ሁልጊዜም አባትዬው አምሽተው በመጡ ቁጥር ጥላሁን በጩኸታቸው ይነቃል። ጥላሁን የአባቱን ድምጽ በደንብ ያውቃል። አቶ አበበ በጨለማ ውስጥ ሲራመዱ ኮቴያቸው በሩ ጋር እስኪደርሱ ይሰማል።
አንድ ምሽት አቶ አበበ ሰክረው እየጮሁ ሲመጡ መንገድ ላይ ጅብ አገኛቸው። አቶ አበበም ''ኡ ኡ! እርዱኝ! ጅብ ሊበላኝ ነው'' እያሉ መጮህ ጀመሩ። አቶ አበበም ሲጮሁ፥ ጅቡ አጠቃቸው።
የሰፈሩ ሰዎች ደግሞ ''ምን አደረግነው እንቅልፍ የሚያሳጣን ይህ ሰካራም!'' እያሉ ሳይመጡላቸው ቀሩ፡፡
ነገር ግን አቶ አበበ ጩኸታቸውን አላቋረጡም ''ኡ ኡ እርዱኝ'' ማለታቸውን ቀጠሉ፡፡ ከዚያም ልጃቸው ጥላሁን ተጠራጠረና ማዳመጥ ጀመረ፡፡ ነገር ግን የአባቱን ኮቴ ለመስማት አልቻለም፡፡
''አባቴ አደጋ ላይ ሳይሆን አይቀርም'' አለ ጥላሁን። ''አሁንስ እያሾፈ አይደለም፡፡''.
ጥላሁን ከአልጋው ዘሎ ወረደ። ምድጃ ውስጥ ተማግዶ የነበረ ፍልጥ ይዞ በፍጥነት ከጎጆው ወጣ።
''አባቴ፥ አባቴ!'' አለ። በጨረቃ ብርሃን፥ አባቱ ከጅቡ ጋ እየታገሉ አያቸው፡፡ ከዛም በእጁ በያዘው ፍልጥ ጅቡን አባሮ አባቱን ታደገ፡፡ ጅቡም ፍልጡን ባየ ጊዜ ሮጦ አመለጠ።.
ከዛን ቀን ጀምሮ አቶ አበበ መጠጥ መጠጣት ተዉ። ለተማሪዎች ተረትና ታሪክ በማስተማር ጊዜያቸውን ማሳለፍ ጀመሩ፡፡
You are free to download, copy, translate or adapt this story and use the illustrations as long as you attribute in the following way:
አባቱን የታደገው ጥላሁን
Author - Kanyiva Sandi
Translation - ከድር ኢብራሂም, ፋሲካ ምንዳ and መዘምር ግርማ
Illustration - Benjamin Mitchley
Language - Amharic
Level - Longer paragraphs
© African Storybook Initiative, 2014
Creative Commons: Attribution 4.0
Source www.africanstorybook.org
Menu
  • Navigate

    Navigate through the story by swiping right or left or clicking when the cursors changes to an arrow on the right or the left edge of the screen.

    Tap or click on the centre of the page to see, or remove the menu bars at the top and the bottom of the screen. You can also use the ESC key.

    You can use the slider at the bottom as a way to move quickly through the story. On a mobile device tap on the slider before you drag the slider button.

    Click or tap to return to African Storybook.

  • Share
    If you have a Twitter or Facebook account, you can share this story on your page or a page you manage. You can also copy the web link (URL) for this story.
    • Twitter
    • Facebook
    • Url
  • Rate
    Other visitors rated this story

    Tell us how much you liked the story – drag the scroller to highlight one or more stars
    • Submit
  • Comment
    Read other people’s comments on the story, or add your own.
    • Enter your comment
    • Name
    • E-mail
    • Post
  • Translations and adaptations
    • Musau saves his father
      English (Original)
    • Musau and his father
      English (Adaptation)
    • Mukiza na se.
      Kinyarwanda (Translation)
    • Mukiza na Se
      Kinyarwanda (Translation)
    • Musa na Se
      Kinyarwanda (Translation)
    • Musau bóyír tàr wov
      Lámnsoʼ (Translation)
    • Kabali ataasa kitaawe
      Luganda (Translation)
    • Amagu Pa Ima Ati
      Lugbarati (Translation)
    • Musalu Awonesa Paapawe
      Lumasaaba (Translation)
    • Musa Ataasa Semwana
      Lunyole (Translation)
    • Musa ni laata we
      Lusoga (Translation)
    • Abalu iko monyonyi ꞌTakaya
      Otuho (Translation)
  • Download to read
    Landscape version
  • Download to print
    Portrait (booklet) version
  • Download EPUB