

በክሪስታል ክላሲክ አካዳሚ ውስጥ ኒሙታባን የሚባል ወጣት ልጅ ነበር።
መሳል ይወድ ነበር፣ ነገር ግን ወላጆቹም ተስፋ ቆርጠውበታል።
ሁሉንም የማስታወሻ ደብተሮቹን ለመሳል ይጠቀም ነበር።
ወላጆቹና መምህራኑ ቀጥተውታል።
ነገር ግን ኒሙታባን መሳል አላቆመም።
ወላጆቹም የትምህርት ቤት አስተማሪዉ የነበሩትን ሚስተር ንጋቮን አመጡለት።
በጣም ደግ ሰው ነበሩ። ኒሙታባን ከትምህርቱ በኋላ እንዲስል ፈቅደዉለታል።
ሚስተር ንጋቮ መጽሐፍትን፣ ሰሌዳዎችን እና ባለቀለም ቀለሞችን እንዲስል አደረገለት።
ኒሙታባን እጅግ በጣም ጥሩ አርቲስት ሆነ። በእያንዳንዱ የትምህርት ቤት ዉጤትም ጥሩ ውጤት አስመዝግቧል።
በየዓመቱ ኒሙታባን በትምህርት ቤቱ የሽልማት ቀን ብዙ ሽልማቶችን ይቀበል ነበር።
ሌሎች ተማሪዎች እሱን ያደንቁታል እና እንደ እሱ መሆን ይፈልጉም ነበር።
ሲያድግም፣ ኒሙታባን በናይጄሪያ ውስጥ ካሉት ምርጥ አርቲስቶች መካከል አንዱ ነበር!
በጣም ጠንክሮ ሰርቶ ብዙ ሽልማቶችን እና ኮንትራቶችን አሸንፏል።
ኒዩሙታባን ለራሱ "ለሌሎች ስነጥበብ ለሚወዱ ነገር ግን የሳይንስ ትምህርቶችን ለመማር ለሚገደዱ ልጆች ምን ማድረግ እችላለሁ?" ብሎ አሰበ።
የኒሙታባን የስነጥበብ ማዕከልን አቋቋመ! በማዕከሉ ልጆች ከትምህርት ቤት በኋላ ስነጥበብን መማር እና ተሰጥኦአቸውን ማዳበር ይችላሉ።
ኒሙታባን አርቲስቶችን ለማበረታታት የስነጥበብ ውድድሮችን አዘጋጅቷል።

