

በትምህርት የመጀመሪያ ቀን፣ ሾላ ረጅም ጥቁር ዘንግ (በትር) ይዞ ነበር።
ሌሎች ተማሪዎች ይህ ነገር እንግዳ (አዲስ) ሆኖባቸዋል።
መምህርት ፊክሌፊ ሾላ (Xola) ዓይነ ስውር ሆኖ እንደተወለደ ለክፍሉ ተማሪዎች አስረዳች።
በትምህርት ቤቱ ውስጥ መንገዱን ፈልጎ ለማግኘት ዘንግ (በትር) እንደሚጠቀምም ገለጸችላቸው።
ተማሪዎቹ ሾላ ለምን ጥቁር መነጽር እንደሚያደርግ መረዳት ጀመሩ።
መምህርቷ በመቀጠል ተማሪዎቹ ሾላን እንደ አንዱ (እንደ እራሳቸው) አድርገው ሊያዩት እንደሚገባ አስረዳች።
ሊዞ እና ሌሎች ወንዶች ልጆች የሾላን ዘንግ (በትር) ለመስረቅ ሲያሴሩ ዞላ በድንገት ሰማቻቸው።
ልጆቹ አዲሱን ተማሪ ለማላመድ (ለመጫወት) ይህ ጥሩ መንገድ እንደሆነ አስበው ነበር።
ዞላ ይህንን ስትሰማ፣ ሾላን ከጉልበተኞች ለመከላከል ሮጣ አጠገቡ ተቀመጠች።
ሊያደርጉት ያሰቡት ነገር የሚያስከትለውን አደጋ ነገረቻቸው። ልጆቹም ለሾላ ከልብ ይቅርታ ጠየቁት።
ጓደኞቹ ተቀምጠው ስለ እግር ኳስ ፍቅራቸው፣ ስለ ስዕል መሳል እና አኒሜሽን (ተንቀሳቃሽ ምስሎችን) ስለ መመልከት ተጨዋወቱ። ከዚህ ውይይት በመነሳት በመካከላቸው ብዙ የሚያመሳስሏቸው ነገሮች እንዳሉ ተገነዘቡ።
ስለ ልዩነቶቻቸውም ጭምር ተጨዋወቱ። ዞላ የጓደኛዋን ጥቁር መነጽር በማድነቅ አሞካሸችው። ይህ ጓደኝነት እርስ በእርሳቸው አድናቆትንና ክብርን የሚሰጡ የእኩዮች ስብስብ (መረብ) እንዲፈጠር አደረገ።
ለሾላ በጣም አስደሳች ቀን ነበር፤ በአዲሱ ትምህርት ቤቱ ውስጥ ከአዲሷ አፍቃሪ ጓደኛው ከዞላ ጋር የደህንነት እና የመልካም አቀባበል ስሜት ተሰማው።

