

በአንዲት ከተማ ውስጥ የሚኖሩ እናት እና ልጅ ነበሩ። እናትየዋ ለልጇ የማትከፍለው መስዋዕትነት አልነበረ ። ከጎረቤት እና ከሰፈር ልጆች እንዳያንስባት የማትችለውን ስራ ሁሉ ትሰራለች።
ልጇ አልአዛርም ጎበዝ ተማሪ ነበርና በየአመቱ ስሟንያስጠራል።አልአዛር የ19አመት ልጅ ነበረ።ምግብ ሲበሉ ሆዷን ጥፍንግ አድርጋ ታስርና ሁለት ጉርሻ ጎርሳ ጠገብኩ ትለዋለች።የሰው ቤት እንጀራ እየጋገረች ፣ልብስ እያጠበች ፣የቀን ስራ እየሰራች ልብስ፣ደብተርና ጫማ ትገዛላታለች።
ገንዘብ ከየት እንዳመጣች አልአዛር ሲጠይቃት ዘመዳቸው እንደሰጣቸው ትነግረዋለች እናም ያምናት ነበር።ታዲያ አልአዛር ወደ ዩንቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና ተፈትኖ ጥሩ ውጤት አምጥቶ አለፈ።
እናቱ በጣም ተቸግራ ነበርና በበፊቱ ስራዋ ቀጥላ ገንዘብ በየ ጊዜው ትልካለች።አልአዛር ተመርቆ ሲመጣ እናቱ ድል ያለ ድግስ ደግሳለች።
አሁንም ብሩ ከየት እንደመጣ ሲጠይቃት እንዳያስጨንቃት እና ዛሬ የደስታ ቀኑ እንደሆነ ትነግረዋለች።ስጦታ የወርቅ ሀብል ስትሰጠው አላመነም።
ማታም ይህ ሁሉ እንዴት እንደሆነ ጠየቃት እሷም እያለቀሰች ዋሸች።ልጇ አልአዛርም አመናት። የምትዋሸው ልጇ አሁንም ልጅ ስለሚመስላት ነበር።
አልአዛር ጥሩ ስራ አገኘ ። ጥሩ ቤት ሰራ ። እናቱን ለልደቱ አምጥቶ በአዲስ ቤት በደስታ እና በተድላ መኖር ጀመረ። ሆኖም ያቺ እናት አሁንም እውነቱን አልተናገረችም ።
ልጇም ጥሩ እና የተደላደለ ህይወት ያኖራት ጀመረ ። በዚህም ቀስ ብላ እውነቱን ነገረችው እና አልአዛር ተከፋ አለቀሰ። ነገር ግን ጎበዝ እና ጠንካራ እናት እንዳለው ሲያውቅ ኩራት ተሰማው ። ለእናቱም ይቅርታ አደረገላት።

