

በደብረብርሃን ከተማ ውስጥ የሚኖር አንድ ልጅ ነበር። ስሙም ሚኪያስ ይባላል። የሚኖረውም ከቤተሰቦቹ ጋር ነበር። ከእለታት አንድ ቀን ጓደኞቹ አብሯቸው ኳስ እንዲጫወት ጠሩት።
እሱም ኳስ መጫወት ይወድ ስለነበር ደስ እያለው እሺ አላቸው። አብረው እየሔዱም በመንገድ ላይ ውሀ እየተንቦራጨቁ ይሔዱ ነበር። ከዚያም ኳስ ሜዳ ደረሱ። ኳስ ሜዳው ጋር ስልክ እንጨት ነበር።
ከስልክ እንጨቱም ጎን ውሀ ነበር። ሚኪያስም ውሀውን አየው። እሱም ሊምቦራጨቅ አስቦ ዘሎ ውሀ ውስጥ ገብቶ ሰመጠ። ጓደኞቹም ከውሀ ውስጥ እንደምንም ብለው አወጡት።
ከውሀ ውስጥም ሲወጣ ልብሱ እርጥብ ሆኖ ነበር። ጓደኞቹ ኳስ ሲጫወቱ እሱ ግን ልብሱ እንዲደርቅለት ፀሀይ ላይ ቁጭ ብሎ ይመለከታቸው ነበር። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ልብሱ ደረቀ። ወደ ቤቱም ተመለሰ።
እቤት ሲገባ ቤተሰቦቹ ፀጉርህና ፊትህ ምን ሆኖ ነው ነጭ የመሰለው ልብስህም ከቤት ስትወጣ ንፁህ ነበር። አሁን ግን የቆሸሸ ይመስላል ምን ሆነህ ነው? ሲሉት እሱም ፈርቶ ኳስ ስጫወት ስለነበር ነው አላቸው።
እነሱም ፊትህንና ፀጉርህን እንዲሁም እግርህን በሳሙና ታጠብ አሉት። እሱም እንደታዘዘው በሳሙና ታጠበ። በቀጣይ ቀን ከእንቅልፉ ሰነሳ ጉንጩ እንደ ሀዘንተኛ ሰው ተጠብሶ ነበር። ልጁም ቤተሰቡም በጣም ደነገጡ።
ቤተሰቦቹም ምንድነው የሆንከው እውነቱን ንገረን አሉት። እሱም በፍርሃት እውነቱን ነገራቸው። ሀኪም ቤትም ሔዶ ተመረመረና መድሀኒት ተሰጠው። ቢሆንም ሙሉ ለሙሉ አልተሻለውም ፊቱና እጆቹ ላይ ጠባሳ አልነበረም።
ግን ሆዱ ላይ ሙሉ ለሙሉ አልተሻለውም ነበር። ይህም የሆነበት ምክንያት ለቤተሰቦቹ አደጋው ሲደርስበት ቶሎ ባለመናገሩና እውነቱን በመደበቁ ነበር።

